፮ ሰንቡላ መሬት ጉጉት (አሞራ)

፮ ሰንቡላ መሬት ጉጉት (አሞራ)

ይህ ኮከብ በመስከረም 7 ቀን ከ2 ከዋክብት ጋራ ከሌሊቱ በ7 ሰዓት ከወደ ፀሐይ መግቢያ የወጣ ነው ፡፡ ሰንቡላ መሬት ቅልቅል መሬት ማለት ነው ሰንቡላ የሰው ይብላ ይባላል በጉጉት አሞራ ይመሰላል ፡፡ ይህ ኮከብ ያለው ሰው በብዙ እንኳ ባይኆን በግንባሩና በቅንድቡ አወራረድ የዓይኑ ቅርፅ የጉጉት ምሳሌ ይገኝበታል ፡፡ ሌሎች የደከሙበትን ገንዘብ ለመውሰድ ሰብሳቢ ዕድል አለው ምክሩ ዘሊቅ ነው ለሰው ይጠቅማል ኑሮው በአገባብ ነው ውሸታምና ጉረኛ ነው መጀመሪያ ይደነግጣል እየቆየ ግን ደፋርና ለበሙሉ ይሆናል የተገባ ምክር የነገር ምላሽ የውቃል በተወለደበት አገር አይኖርም በቀይ ቦታ ይኑር ነጭ ነገር ክፍሉ ነው ከዘመዶቹ ጋር አይስማማም በነገር አይረታም ሕልሙ እሙን ነው ቶሎ ይደርሳል ሲሳ ብዙ ነው ሰውን ማሞኘት ይችላል አጭበርባሪና ብልጥ ነው ክፍሉ ከተማ ነው ገጠር አይሆነውም ሹመት ያገኛል ሳቅ ያበዛል እግዚአብሔርን ያምናል ጸሎቱ ሥሙር ነው በጊዜ ወደቤቱ መግባት አይሆንለትም ያልደረሰበትና የማያውቀው አገር የለም ፊቱን ጥክ አድርገው ቢያዩት አይችልም ፊቱን ያዞራል ከትልክ ሰው ጋራ ሲነጋገር ይጃጃል የአሰበውን ትቶ ያላሰበውን ይናገራል የሰው መውደድ አለው ስጦታና ሽልማት ለማግኘትዕድላም ነው ተልኮ ጉዳይ ማከናወን ይሆንለታል በዘንግ ቆሞ አይችልም ተቀምጦ ሲመክር አዋቂ ነው ፡፡

ሰፊ ዝና አለው ከሰው ገር በቶሎ አይላመድም ሰላማዊ አንኳ ቢሆን ነገር ወደአለበት ፈልጎ ይገባል ሰበውን ትቶ ያላሰበውን ይናገራል ወዳው ደግሞ ይጠጠታል በብዙ ነገር እድለኛ ነው ነገር ግን ዕድሉን በገዛ ራሱ ያጠፋዋል ወደኋላ ጊዜው ጥቅሙን አባራሪ እንጀራውን ገፊ ይሆናል የሕፃን ሽማግሌ ነቱን በወራዳነት ይለውጠዋል የጠላቶቹን መውደቅ ያያል ፡፡ ቅንዝረኛ ነው ፡፡ ኃያል እልከኛ ቶሎ ተቆጭ አትነኩኝ ባይ ነው ነገር ግነ አጭሮ አይጣላም ልጆች ይወለዳል ሰውን ማማት ይጠላል ጠላቱ ብዙ ነው ፊቱ ክፍት ቀላል ድምጹ ከባድ ሆኖ ብትን ነው ፡፡ ሴት መድኃኒት ታበላዋለች በ27 ዓመቱ መቅሰፍት ያስፈራዋል ጭኑን ይቀረጥመዋል ራሱን ብለቱን ወገቡን ሆዱን እየነፋ ያመዋል ፡፡ መድኃኒቱ ነጭ ወይንም ቀይ በግ አርዶ በደሙና በፈርሱ ይታጠብ ዓሳና ሰሊጥ በዛጎልማ ዶሮ አሰርቶ ይብላ መረቁንም ይጠጣ ፡፡

ለሆዱ በሸታ ደግሞ የበግ ላትና ደረቅ ጠጅ ቁንዶ በርበሬ ኤፍራን ቀለም የአሞሌ ጨው አንድ ጽዋ ቅባኑግ ነጭ ሽንኩርት በቶፋ መርጎ 3 ቀን ከበበላዩ እሳት አንድዶ ማር እየበላ ይጠጣው በነጭ በግ ብራና ጸሎተ ንድራን ትምህርተ ኅቡዓትን እና መስጥመ አጋንንትነረ አስጽፎ ይያዝ ፡፡ የምስርችና የፍለ ፈጅ የግዜዋና የቁራ አረግ በአድስ ቅል ዘፍዝፎ ኪዳንና ትምህርተ ኅቡዓትን አስደግሞ ይታጠብ ፡፡

ከዘመን ማርቆስ ከወሮ ታኅሣሥና መጋቢት አይሆኑትም በጥርና ሰኔ ድንገት በሽታ ያገኘዋል ለዚህ መድኃኒቱ ጭቁኝ ነጭ ሽንኩርት ቁንዶ በርበሬ ጫት ቡና አንድነት እያፈላ እስከ 7 ቀን ይጠጣ ዕጣን ያጢሥ ኮከቡ አምልኮ ይወዳል የቀይ ከላድማ ፍየል ወይም ቀይ በግ ጭዳ ያድርግ ፡፡ ከሚፈላው መድኃኒት አትርፎ በቀይ ዶሮ ደም አጥምቶ (ነክሮ) ክንፉን ጨምሮ 3 ቀን ይታጠን ፡፡ በበገግ ብራና መእሰረ አጋንንት ና 4ቱ ኤኮሳትን ሱስንዮስንና ጸሎተ ንድራን አልቦ ስምን ዓይነወርቅን አስማተ ሰሎሞንን አስጽፎ ይያዝ ፡፡ የዘመድ ጠላት በፍየል ሥጋ መድኃኒት ያደርግበታል በዘመነ ማርቆስ ረቡዕ ቀን በ37 ኣመቱ በጭንቅ ይታመማል፡፡ እስከ ሞት ይደርሳል ወደ ፈታሪው አጥብቆ የለመነ ያዘነ የተከዘ እንደሆነ ግን ዘመኑ 69 ይሆናል ፡፡ ፀረ ኮከቦቹ ሐመል ደለዊ አሰድ ናቸው ግጥሙ ቀውስ ሑት ገውዝ ፡፡ ማእከላዊ ሚዛን ጀዲ ሠውር ናቸው ክረምት ይሆነዋል የሰው ገንዘብ ይገባለታል ጥቁር ነገር አይወድለትም ግጥሙ ቀይ ነገር ነው እጀ ሰብእ የፃረረዋል ከዛሮች ብር አለንጋ ከውላጅ መቅረጭ ዋስ አጋች የመለከቱታል ከአውሬና ከቁስል የተነሣ የስፈራቃል ክፍለ ዕዳው ቡሃ በግ ቀይ በግ ነው ፡፡ ዓርብና ሮብ አይሆኑትም ሰኞ ማክሰኞና ሐሙስ ቅዳሜ ግጥሙ ነው የሚሆነው ፈረስ ዳማ ሶቄ ቃጫ ቦራ ነው ፡፡

ሰንቡላ መሬት ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ ፡፡

ዓይነ ዘማ ቅንዝረኛ ለኁሉ እሽ ባይ ወራዳ እግረ ቀጭን ትኩሳታም ትሆናለች ትካዜ ይገባታል ዓለማዊ ባካና ናት አይሞላላትም መላሷ ተናጋሪ አፈ -ደረቅ ዓቅሟ ደካማ ቀናተኛ ሕመም አያጣትም ነገር ግን አይበረታባትም ዓይነጥላ ገርጋሪያት አለባት በቀይ በግ ብራና አልቦ ስምን አስጽፋ ትያዝ ጥቁር ፍየል አሳርዳ ደሙን ቀድታ ከባህር ዳር ይዛ ሒዳ ትታጠብበት ትንሽ ቀና ብላ በውሃው ትለቅል መብል መጠጥ ትሰጣለችገንዘብ አተሰጥም ትነፍጋለች ዓይንና ጥርሷ መልከ መልካም ናት ወንድ መኰንን ይወዳታል ቃለ ልስልስ ናት ሆዷን ጐኗን ያማታል ሥጋ ስትበላ የሰው ዓይን ያስፈራታል ትጠንቀቅ ፡፡