የወልቃይት አማራ የቅማንትና የአገው አማራዎች

 የወልቃይት አማራ የቅማንትና የአገው አማራዎች ልብ ያለው ልብ ይበል !

Tinsae Hager

ወያኔ በአማራ ክልል ላይ የዘረጋው ምስጢራዊ ሴራ (በቅርብ የደረሰን አዲስ መረጃ ይነበብ)

የህወሀት የምንግዜም ስጋትና ፍርሃት አማራ ክልል እንደሆነ የትግራይ ባለስልጣናት በተለያየ መድረክ ሲናገሩት ኖረዋል፡፡ይህንን ስጋት ለመቀነስና ታላቋን የትግራይ ሪፐብሊክ ለመመስረት የነደፉት ስልት አማራን እርስ በእርሱ ከአጣሉ በኋላ ግማሹን የአማራ መሬት በሃይል ወደ ትግራይ ክልል መውሰድ ነው፡፡ከተወሰዱት የአማራ ክልል መሬቶች በተጨማሪ እነዚህ በሃይል ለመወረር እቅድ የተያዘባቸው ቦታዎች የቅማንት አማራዎች እና የአገው አማራዎች ናቸው፡፡

 የወልቃይትአማራ የቅማንትና የአገው አማራዎች

ይህንን የመውረር ስትራቴጅ የነደፉት አቶ ስብሃት ነጋ እና አባይ ጸሃይየ ሲሆኑ የመጀመሪያው እርምጃ ወደቅማንትና አገው ኗሪዎች ትግሬዎችን በማስገባትና አንዳንድ አዳሪ ሰዎችን ከተላጆቹ በመምረጥ በስልጣንና በገንዘብ በማታለል አማራን እርስ በእርስ ከአጋጩ በኋላ ሲዳከምላቸው ራሳቸውን የአጋው አማራዎችንና የቅማንት አማራዎችን በወረራ ወደ ትግራይ ለማስገባት ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተደርሶበታል፤‹‹

እነዚህን የአገውና የቅማንት አማራዎች ከሌላው ብዙ የአማራ ክልል ህዝብ በጠብ ከነጠልናቸው የሚረዳቸው ስለሌለ በሃይል ወደ ትግራይ ለማስገባት ከህጻን እጅ ከረሚላ የመንጠቅ ያህል ቀላል ነው፤ይህን ምቹ ጊዜ ተጠቅመን ከአማራ መሬት ቆርሰን ወደ ትግራይ ክልል የማንወስድ ከሆነ ትግራይ ለመኖር አትመችም›› ሲሉ ስብሀት ነጋ እንደተናገሩ መረጃው ያመለክታል፡፡

ከሁሉም ቅማንት ላይ ትኩረት ያደረጉ ሲሆን ከሌሎች አማራዎች ጋር በማጋጨት ረዳትና አቅም ከኣሳጡ በኋላ በወረራ ለመያዝ ከመታቀዱ በተጨማሪ አጼ ቴወድሮስ ከቅማንት አማራዎች የተወለደ ነው በማለትና ከሌሎች አማራ ክልል ተወላጆች በመነጠል የቴዲ ዘር እያለ እንቅልፍ ያሳጣቸውን ሰፊውን አማራ ወኔ ለማሳጣት እንደሆነ መረጃው ይገልጣል::

በተለይ አሁን አማራ ወልቃይትን ለማስመለስ ወጥሮ ስለያዛቸው አቅጣጫውን ለማስቀየር ለትግሬ ተወላጅ ጋዜጠኞቹና ለባለስልጣናት በእየተገኘው አጋጣም ፌስቡክን ጨምሮ የቅማንትን ጉዳይ እንዲያራግቡና ስለ ወልቃይት ግን ማንም ማውራት እንደሌለበት ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ ሰጠዋል፡፡ሸገር እሬዲዮ ስለወልቃይት መረጃ ሲጠይቅ አናውቅም የሚል መልስ የተሰጠበት ምክንያትም ከእዚሁ ጋር ተያይዞ ነው፡፡

ለትግሬ ጋዜጠኞች ግማሾቹ ስለ ቅማንት በፌስቡክ ሲጽፉ ሌሎቹ ሼር በማድረግ እንዲያሰራጩ መመሪያ የተሰጡ ሲሆን ስለቅማንትም ይሁን ስለሌላ ተጽፎ ብታዩ ጸሃፊዎቹም ሆኑ አስተጋቢዎቹ የትግሬ ተወላጆች እንደሆኑ እንድትገነዘቡ እናሳስባለን፤እናንተም ይህንንም መረጃ ሼር በማድረግ ለሌላው አድርሱ:: ላልሰማው አሰሙ፡፡

ድል ለሰፊው ህዝብ!

Tinsae Hager