የሁለት ሺህ ስምንት ትንሳኤ (ፋሲካ) በአል በለንደን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በስጋት ተከብሮ ዋለ

የሁለት ሺህ ስምንት ትንሳኤ (ፋሲካ) በአል በለንደን ርእሰ አድባራት ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዉስጥ በስጋት ተከብሮ ዋለ ። ችግሩ የተፈጠረው የቀድሞው የስራ አመራር አባላት ተከታዮች የብዙሃኑን አባላት ከሌሊቱ ስድስት ሰአት (12:00 AM) ላይ ቅዳሴ ጸሎት ባግባቡ ሳይጨርሱ እንዲወጡ ግፊት በማድረጋቸው ነው።

የሁለት ሺህ ስምንት ትንሳኤ(ፋሲካ)በአል በለንደን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በስጋት ተከብሮ ዋለይህ በትንሳኤ ለት መተዛዘን ሲገባ ስርአተ ቅዳሴ ሳያልቅ እንዲወጡ መጠየቅ ከፍተኛ ሃዘንና ዉጥረትን ፈጥሮ አድሮአል። ለዝርዝሩ ተንቀሳቃሽ ምስሉንና በአማርኛና በእንግሊዝኛ በፊደል የተሳፈዉን ጽሑፍ ይመልከቱ። በተጨማሪም አቶ ሸንቁጥ አየለ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ሁከት በሚመለከት የጻፉትንም ሃይማኖታዊ ትንተና አካተናል።

 

 

 

 

Ethiopians celebrated Easter (ፋሲካ) in London Amid Mixed Feelings at the Battersea Reese Adbarat St Mary of DebreTsion Ethiopian Orthodox Church. The mixed feelings were caused by the ex-trustees group who complained through its Lawyers and asked the majority members to evacuate the Church at 12:00 am (between 30 April and 01 May 2016) which is too early to complete TSELOTE KIDASE and other services (Prayers).

When the Majority members representatives released a press statement regarding the change of the Easter Church service programme the mood of many people have been changed. Many Church and other Ethiopian community members have also been saddened by this unnecessary and irresponsible actions which can escalate the de-escalated tensions between the two parties. Easter is supposed to be a time of compassion and reconciliation but unfortunately Ethiopians and their friends in London unable to see such good deeds.

However, the TSELOTE KIDASE and other services were provided quite well inside the church within the given time.This video clip shows the services presented by the majority members clergy inside the church and the tension between the two contesting fellow Ethiopian groups when the church was evacuated. Thanks to the area Police who arrived on time and kept peace and order at the gate.

 


ሸንቁጥ አየለ

5 hrs ·

የዘንዶዉ መንፈስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች መሃከል ሰላም እና አብሮ ማምለክ እንዳይኖር ለምን ፈለገ? በለንደን የተከናወነዉን የዘንድሮዉን የትንሳዔ በዓል ገጽታ እንደማሳያ

——————————————————
-ዘንድሮም የትንሳዔ በአል በለንደን ክርስቲያኖች ዘንድ በልዩነት: ተኮራርፎ በማምለክ: እና አንድን ቤተክርስቲያን ከዚህ እስከዚህ ሰዓት እኛ ቀሪዉን እናንተ በሚል አሳዛኝ ሁኔታ እንዲያልፍ ተደርጓል::

-በሚያሳዝን መልኩም አንዱ ወገን አንዱ በፖሊስ ሀይል የጸሎት ስነስርአቱን ባልጨረሰበት ሁኔታ ሰዓቱ ደረሰ : ፍርድ ቤት የገደበላችሁ ሰዓት ይሄን ያህል ነዉ በመባባል በክርስቲያኖች መሃከል ሳይሆን በአህዛብ መሃከል የማይገባ ድርጊት እና ጥላቻ ሲራመድ ተስተዉሏል::

-ከዚህ ሁሉ የክርስቲያኖች መለያዬትና ጸብ ጀርባ ደግሞ በዘንዶዉ መንፈስ የሚመራዉ ሀይል ቆሟል:: አንዱን ወገን በመወገን : ቡድነኝነትን በማበረታታት: በአማኞች መሃከል ፖለቲካዊ ጥላቻን በመዝራት: እክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዉስጥ የዲያቢሎስ ስራ የሆነዉ የዘር ቆጠራ እንዲገባ በማድረግ: ጳጳስ ሳይሞት ጳጳስ አይሾምም የሚለዉን የቤተክርስቲያኗን ህግ በመሻር: የቤተክርስቲያኗን ሲኖዶስ በመቆጣጠር እና ክርስቲያኖች እንዳይግባቡ በማድረግ የዘንዶዉ መንፈስ የተሳፈረባቸዉ ሀይሎች ሁሉንም ክፋትና ወንጀል በክርስቶስ ቤተክርስቲያን ላይ ፈጽመዉባታል::

————————————————————-
-በኢትዮጵያዉያን ብሄረሰቦች መሃከል የተዘራዉ የጥላቻ መርዝ ያለ ምክንያት አይደለም:: ኢትዮጵያን ለማጥፋት እንጅ::ለምሳሌም በኦሮሞ እና በአማራ ማህበረሰብ መሃከል ወያኔ የሰነጠቀዉን የጥላቻ ስንጥቅ ለመድፈን አሁን ያሉት ፖለቲከኞች ሁሉ ካቅማቸዉ በላይ እስኪሆን ድረስ ወደ ሰማይ እንዲጉን አድርጎታል::በትግሬ እና በአማራ ህዝብ መሃከል አለመተማመን ፈጽሞ እንዲሰፍን ከበሮ ሲደልቅ የኖረዉ ወያኔ የቤት ስራዉ ተሳክቶለታል::በኦሮሞዎችና በሶማሌዎች መሃከል: በኦሮሞዎች እና በሲዳማዎች መካከል: በኦሮሞዎች እና በትግሬዎች መሃከል: በአኝዋክና በንዌር መሃከል: በሶማሌና በአፋር መሃከል እንዲሁም በብዙ ኢትዮጵያዉያን ማህበረሰቦች መሃከል ጥላቻ እና መለያዬትን በደንብ አድርጎ ወያኔ ዘርቷል::

-ይባስ ብሎም ሙስሊም ኢትዮጵያዉያን እና ክርስቲያን ኢትዮጵያዉያን አብረዉ እንዳይኖሩ ገና ስልጣን ላይ ሲፈናጠጥ ወያኔ በርካታ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳዎችን ሰርቷል:: በጣም እጅግ በጣም የተሳካለት የልዩነት ስብከቶችን በደንብ አድርጎ በትዉልዱ ዉስጥ ረጭቷል::

-ኦርቶዶክ ተዋህዶ ፈጽሞ ትወድም ዘንድ አንዴ የአማራ ብቻ ነች: አንዴ የትግሬ ነች: አንዴ የጉራጌ መሸሸጊያ ነች እያለ ኦርቶዶክስ ኢትዮጵያዉያን የመጨረሻ እንዲጠላሉ እና እምነቷም እንድትጠፋ ሁሉንም ስራዎች ሰርቷል::አሁንም እየሰራ ነዉ::

– ዉጊያዉ መንፈሳዊ ነዉ::ኢትዮጵያ እምትባል ሀገር እንድትኖር የማይፈልገዉ ዘንዶዉ ነዉ:: በህዝባችን መሃከል ጥላቻ እንዲነግስ የሚታገለዉ ዘንዶዉ ዋና አላማዉ በምድር ላይ የእግዚአብሄር በአላት የማይታሰብበት: የእግዚአብሄር ምልክት የጠፋበት የአዳም ዘር ለመፍጠር ነዉ:: ወያኔን የተሳፈረዉ ርኩስ መንፈስ ይሄዉ የዘንዶዉ መንፈስ ነዉ::የዘንዶዉ መንፈስ ጥላቻ እና ልዩነት ዋናዉ መገለጫዉ ነዉ::

– እግዚአብሄር እቅዱ ግን ሌላ ነዉ:: የእግዚአብሄር እቅድ ግን የዘንዶ እራስን መቀጥቀጥ ለኢትዮጵያ ሰዎችም መንፈሳዊ ሀይልን ማልበስ (ይሄን ሲያመሰጥረዉም ምግብ መስጠት ይለዋል) ብሎም የእግዚአብሄር ምልክት እና መታሰቢያ ከአዳም ልጆች እንዳይጠፋ ኢትዮጵያን ምክንያት ማድረግ ነዉ:: ኢትዮጵያም ፈጽሞ አትጠፋም::የእግዚአብሄር ናትና:: በኢትዮጵያዉያን መሃከል ሁሉ የተዘራዉ ጥላቻ ይሻራል::

—–
መዝሙር 74 ይሄን መንፈሳዊ ዉጊያ እንዲህ ይተርከዋል::
3. ጠላት በቅዱሳንህ ላይ እንደ ከፋ መጠን፥ ሁልጊዜም በትዕቢታቸው ላይ እጅህን አንሣ። 4. ጠላቶችህ በበዓል መካከል ተመኩ፤ የማያውቁትንም ምልክት ምልክታቸው አደረጉ። 5. እንደ ላይኛው መግቢያ ውስጥ በዱር እንዳሉም እንጨቶች፥ በመጥረቢያ በሮችዋን ሰበሩ። 6. እንዲሁ በመጥረቢያና በመዶሻ ሰበሩአት። 7. መቅደስህን በእሳት አቃጠሉ፤ የስምህንም ማደሪያ በምድር ውስጥ አረከሱ። 8. አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው። ኑ፥ የእግዚአብሔርን በዓሎች ከምድር እንሻር አሉ። 9. ምልክታችንን አናይም ከእንግዲህ ወዲህም ነቢይ የለም፤ እስከ መቼ እንዲኖር የሚያውቅ በኛ ዘንድ የለም። 10. አቤቱ፥ ጠላት እስከ መቼ ይሳደባል? ስምህን ጠላት ሁልጊዜ ያቃልላልን? 11. ቀኝህን በብብትህ መካከል፥ እጅህንም ፈጽመህ ለምን ትመልሳለህ? 12. እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፥ በምድርም መካከል መድኃኒትን አደረገ። 13. አንተ ባሕርን በኃይልህ አጸናሃት፤ አንተ የእባቦችን ራስ በውኃ ውስጥ ሰበርህ። 14. አንተም የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ፤ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው።
—————-
እናም የእግዚአብሄር እቅድ የዘንዶ እራስን መቀጥቀጥ ለኢትዮጵያ ሰዎችም መንፈሳዊ ሀይልን ማልበስ (ይሄን ሲያመሰጥረዉም ምግብ መስጠት ይለዋል) ብሎም የእግዚአብሄር ምልክት እና መታሰቢያ ከአዳም ልጆች እንዳይጠፋ ኢትዮጵያን ምክንያት ማድረግ ነዉ:: ኢትዮጵያም ፈጽሞ አትጠፋም::የእግዚአብሄር ናትና::
—-

ወደ ሮሜ ሰዎች
3፥22
እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤

10፥12
በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
——–
በለንደን በዘንድሮ በዓል ላይ የተከሰተዉን አሳዛኝ የልዩነት ክስተት ለመመልከት ከዚህ በታች ያለዉን ቪዲዮ ይጫኑ