በመኢአድ አመራሮች ላይ የተደረገዉን ግድያ ሙከራ የሚያወግዝና ተቃዋሚዎች በጋራ ሊወስዷቸዉ ስለሚገቡ እርምጃዎች የተደረገ ዉይይት

በመኢአድ አመራሮች ላይ የተደረገዉን ግድያ ሙከራ የሚያወግዝ ብሎም ተቃዋሚዎች በጋራ ሊወስዷቸዉ ስለሚገቡ ነጥቦች የተደረገ ዉይይት

በመኢአድ አመራሮች ላይ የተደረገዉን ግድያ ሙከራ የሚያወግዝ ብሎም ተቃዋሚዎች በጋራ ሊወስዷቸዉ ስለሚገቡ ነጥቦች የተደረገ ዉይይት——————በማንኛዉም ተቃዋሚ ድርጅት ላይ የሚደረገዉ ወከባ እና አፈና የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት እና የዲሞክራሲ ጥያቄ ያፈጥነዉ እንደሆነ እንጂ ሊያኮሰምነዉ ከቶም አይችልም::–መኢአድ በኢትዮጵያ ዉስጥ ለሰላሳ አመታት በኢትዮጵያ ዉስጥ ሲደረግ የነበረዉን የዲሞክራሲ: የነጻነት: የፍትህ እና የአንድነት በዋነኛ ተቃዋሚነት ሲመሩ የነበሩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የተሰባሰቡበት ሀይል ነዉ:: በመኢአድ ላይ የሚሰነዘር ማንኛዉም አይነት ጥቃት በኢትዮጵያ የዲሞክሲ የፍትህ እና የነጻነት ጥያቄዎች ሁሉ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት ነዉ::—በመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ፕሬዝዳንት በአቶ ማሙሸት አማረ እና በም/ፕሬዝዳንቱ በአቶ አብርሃም ጌጡ የተደረገዉ የማዋከብ እና የመግደል ሙከራ የመኢአድ አባላት: በመላዉ አለም ያሉ ደጋፊዎች እንዲሁም መላዉ የኢትዮጵያ የነጻነት ሀይላት ሁሉ በጋራ ሊያወግዙት የሚገባ ወንጀል ነዉ በሚል መነሻ ሀሳብ የተዘጋጀ ዉይይት:: ————የዉይይት ነጥቦች——-1. የመኢአድን አመራሮች ላይ እየተደረገ ያለዉ የወከባ እና የመግደል ሙከራ በነገዉ የኢትዮጵያ የዲሞክራሲ እና የአንድነት ጥያቄ ሂደት ዉስጥ ምን አንደምታ ይኖረዋል? 2. በአንድ አመት ዉስጥ በመኢአድ አመራሮች ላይ የግድያ ሙከራ ሲደረግ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዉ መሆኑ ነዉ? ይሄ ምንን ያሳያል? መኢአድ ላይ ለምን እንዲህ አይነት ትንኮሳዎች ተደጋገሙ? 4.እነ ጀዋር በርካታ ዜጎችን አርደዉ: ብዙ ቤተክርስቲያን አቃጥለዉ: በርካታ ህዝብ እንዲፈናቀል አድርገዉ በነጻነት በሚንጎማለሉበት ሀገር እንዲሁም ስለ ነገዉ እንምከር ብሎ መንግስት ፓርቲያቸዉን ለዉይይት ጋብዟል::በዉይይቱም ላይ የጀዋር ፓርቲ መሪዎች እነ መራራ ተሳትፈዋል::ሆኖም ፍጹም ሰላማዊ የመኢአድ ታጋዮች በነጻነት ወጥተዉ እንዳይገቡ ተደጋጋሚ የመግደል ሙከራዎች እየተደረገባቸዉ ነዉ:: ይሄ ምን ያሳያል? 5. ይሄ የተቃዋሚ መሪዎችን የመግደል ሙከራ ትግሉን ለማሸማቀቅ ብሎም ዘረኛ አምባ ገነን ስርዓትን ፍጽሞ ለማስፈን የታቀደ የወደፊት እቅድ ነጸብራቅ ማለት ይቻላል? ሰላማዊ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን መድረክ መንግስት የሚያጠበዉ ከሆነ ቀጣዉ የትግል ስልት ምን ሊሆን ይችላል?6. ሰሞኑን አቢይ ከመስከረም 30 ብኋላ ስለሚኖረዉ የመንግስት ይዘት እና ቅርጽ ለመምከር በጠራዉ የዉይይት ፕሮግራም ላይ መኢአድን: ባልደራስን; አዴሃንን: አብንን: እንዲሁም ሌሎች የአማራ ድርጅቶችን እና በርካታ የኢትዮጵያ አንድነት አቀንቃኝ ድርጅቶችን ሳይጋብዝ አግልሏቸዋል::ከዚያ ይልቅ ኦነጋዉያንን ብቻ ሰብቦ በሀገር ጉዳይ ላይ መከርኩ ሲል ቀልዷል:: የዚህ አካሄድ ትርጉሙ ምንድን ነዉ?የነገዋ ኢትዮጵያን ወዴት ሊወስዷት ነዉ የታሰበዉ?7. ይሄን አምባ ገነን እና ዘረኛ ስርዓት በጋራ ለመታገል እዉነተኞቹ የኢትዮጵያ የነጻነት እና የዲሞክራሲ ሀይላት (በኢትዮጵያ አንድነት የተሰለፉትም: በአማራ ድርጅት የተሰለፉትም) ወደፊት ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል? የጋራ ትልቅ የመግባቢያ አጀንዳ ለመቅረጽስ ለምን ተቸገሩ?

Posted by አማራ ሚዲያ ማዕከል / Amara Media Center on Sunday, May 10, 2020
በመኢአድ አመራሮች ላይ የተደረገዉን ግድያ ሙከራ የሚያወግዝ ብሎም ተቃዋሚዎች በጋራ ሊወስዷቸዉ ስለሚገቡ ነጥቦች የተደረገ ዉይይት
በመኢአድ አመራሮች ላይ የተደረገዉን ግድያ ሙከራ የሚያወግዝ ብሎም ተቃዋሚዎች በጋራ ሊወስዷቸዉ ስለሚገቡ ነጥቦች የተደረገ ዉይይት
—————-

–በማንኛዉም ተቃዋሚ ድርጅት ላይ የሚደረገዉ ወከባ እና አፈና የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት እና የዲሞክራሲ ጥያቄ ያፈጥነዉ እንደሆነ እንጂ ሊያኮሰምነዉ ከቶም አይችልም::

–መኢአድ በኢትዮጵያ ዉስጥ ለሰላሳ አመታት በኢትዮጵያ ዉስጥ ሲደረግ የነበረዉን የዲሞክራሲ: የነጻነት: የፍትህ እና የአንድነት በዋነኛ ተቃዋሚነት ሲመሩ የነበሩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የተሰባሰቡበት ሀይል ነዉ:: በመኢአድ ላይ የሚሰነዘር ማንኛዉም አይነት ጥቃት በኢትዮጵያ የዲሞክሲ የፍትህ እና የነጻነት ጥያቄዎች ሁሉ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት ነዉ::

—በመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ፕሬዝዳንት በአቶ ማሙሸት አማረ እና በም/ፕሬዝዳንቱ በአቶ አብርሃም ጌጡ የተደረገዉ የማዋከብ እና የመግደል ሙከራ የመኢአድ አባላት: በመላዉ አለም ያሉ ደጋፊዎች እንዲሁም መላዉ የኢትዮጵያ የነጻነት ሀይላት ሁሉ በጋራ ሊያወግዙት የሚገባ ወንጀል ነዉ በሚል መነሻ ሀሳብ የተዘጋጀ ዉይይት::

————
የዉይይት ነጥቦች
——-
1. የመኢአድን አመራሮች ላይ እየተደረገ ያለዉ የወከባ እና የመግደል ሙከራ በነገዉ የኢትዮጵያ የዲሞክራሲ እና የአንድነት ጥያቄ ሂደት ዉስጥ ምን አንደምታ ይኖረዋል? 

2. በአንድ አመት ዉስጥ በመኢአድ አመራሮች ላይ የግድያ ሙከራ ሲደረግ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዉ መሆኑ ነዉ? ይሄ ምንን ያሳያል? መኢአድ ላይ ለምን እንዲህ አይነት ትንኮሳዎች ተደጋገሙ? 

4.እነ ጀዋር በርካታ ዜጎችን አርደዉ: ብዙ ቤተክርስቲያን አቃጥለዉ: በርካታ ህዝብ እንዲፈናቀል አድርገዉ በነጻነት በሚንጎማለሉበት ሀገር እንዲሁም ስለ ነገዉ እንምከር ብሎ መንግስት ፓርቲያቸዉን ለዉይይት ጋብዟል::በዉይይቱም ላይ የጀዋር ፓርቲ መሪዎች እነ መራራ ተሳትፈዋል::ሆኖም ፍጹም ሰላማዊ የመኢአድ ታጋዮች በነጻነት ወጥተዉ እንዳይገቡ ተደጋጋሚ የመግደል ሙከራዎች እየተደረገባቸዉ ነዉ:: ይሄ ምን ያሳያል? 

5. ይሄ የተቃዋሚ መሪዎችን የመግደል ሙከራ ትግሉን ለማሸማቀቅ ብሎም ዘረኛ አምባ ገነን ስርዓትን ፍጽሞ ለማስፈን የታቀደ የወደፊት እቅድ ነጸብራቅ ማለት ይቻላል? ሰላማዊ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን መድረክ መንግስት የሚያጠበዉ ከሆነ ቀጣዉ የትግል ስልት ምን ሊሆን ይችላል?

6. ሰሞኑን አቢይ ከመስከረም 30 ብኋላ ስለሚኖረዉ የመንግስት ይዘት እና ቅርጽ ለመምከር በጠራዉ የዉይይት ፕሮግራም ላይ መኢአድን: ባልደራስን; አዴሃንን: አብንን: እንዲሁም ሌሎች የአማራ ድርጅቶችን እና በርካታ የኢትዮጵያ አንድነት አቀንቃኝ ድርጅቶችን ሳይጋብዝ አግልሏቸዋል::ከዚያ ይልቅ ኦነጋዉያንን ብቻ ሰብቦ በሀገር ጉዳይ ላይ መከርኩ ሲል ቀልዷል:: የዚህ አካሄድ ትርጉሙ ምንድን ነዉ?የነገዋ ኢትዮጵያን ወዴት ሊወስዷት ነዉ የታሰበዉ?

7. ይሄን አምባ ገነን እና ዘረኛ ስርዓት በጋራ ለመታገል እዉነተኞቹ የኢትዮጵያ የነጻነት እና የዲሞክራሲ ሀይላት (በኢትዮጵያ አንድነት የተሰለፉትም: በአማራ ድርጅት የተሰለፉትም) ወደፊት ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል? የጋራ ትልቅ የመግባቢያ አጀንዳ ለመቅረጽስ ለምን ተቸገሩ?